የቢሮዉ ሀላፊዉ መልዕክት
ሲዳማ ብህራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ
አቶ በየነ ባራሳ ባላንጎ የቢሮ ህላፊ ምልአክት
ትምህርት የሀገራትን የእድገት ደረጃና ፍጥነት ከመወሰን አኳያ የራሱን ድርሻ የሚወጣ ትልቅ ዘርፍ ነው። በአለም ላይ የሚገኙ ሀገራት አሁን ያሉበት የእድገት ደረጃ ላይ የደረሱት ትምህርት ላይ በሰሩት ስራ ነው። የበረቱትም የታላቅነታቸው መንስኤና ወደ ኋላ የቀሩትም ቢሆኑ በትምህርት ላይ በሰጡት ትኩረት ልክ ነው።
ትምህርት ትውልድን ብቁ እንደዚሁም ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በማድረግ የሀገራት እድገት ያፋጥናል። ይህንን መነሻ በማድረግ ሀገራት ትኩረት ሰጥተው በሚሰሩት ስራ ውስጥ አንዱና ትልቁ ትምህርት ነው። ሀገራችን ኢትዮጵያም በተለያዩ ጊዜያት ትምህርት ላይ ማሻሻያዎችን በመስራት ርብርብ ስታደርግ ቆይታለች። በአሁኑ ጊዜም አዲስ የትምህርት ፖሊሲ በመቅረፅ ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር የሚሄድ ዘመናዊ ትምህርት ለመስጠት የሚስችል የስርአተ ትምህርት ለውጥ አድርጋ በመረባረብ ላይ ትገኛለች።
የሲዳማ ብሔሪዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮም ሀገራዊ የትምህርት ፖሊሲ ለውጥ መሰረት በማድረግ የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ “የሲዳማ ስርአተ ትምህርት ማሻሻያ” ሚለውን ክልላዊ ፕሮግራም በማቋቋም ዘላቂ የዕድገት ምንጭ ለመፍጠር “የሲዳማ ትምህርት ማሻሻያ ፈንድ” በህግ በማፀደቅ በሁሉም ህብረተሰብ ተሳትፎ በትምህርት ችግሮችን የሚፈቱና ተወዳዳሪ ዜጎችን በመፍጠር በክልሉ ማህበረሰባዊ ለውጥ ለማምጣት ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ ይገኛል።
የትምህርት ችግሮችን ከመሰረቱ ከመፍታት አኳያ የማያቋርጥ ጥረት በማድረግ የክፍለ ዘመኑን ትምህርት በክልላችን ለሚገኙ ዜጎች በማዳረስና ሁለንተናዊ ዕድገት ከማረጋገጥ አንፃር ሁላችንም እንዝመት እያልኩ ለሲዳማ ብሔር ብሩኅ ተስፋ እንዲፈነጥቅ ልባዊ ምኞቴን እገልጻለሁ።
የምሰጡ አገለግሎቶች
ዜናዎች


Supple use of heads message The goal of adult and non-formal education is to provide basic adult education to the youth and adults aged 15 years and above, to enable the adult to be able to read, write and calculate, and to provide non-formal education programs for children and youth who do not h

Supple use of heads message The goal of adult and non-formal education is to provide basic adult education to the youth and adults aged 15 years and above, to enable the adult to be able to read, write and calculate, and to provide non-formal education programs for children and youth who do not h
ፎቶ/ስዕል